ሉፄ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት በኮይሻ




አቶ ደግፌ ኃ/ማርያም ለመላው የጎፋ ዕድገትና ልማት ማህበር አባላትና ደጋፊዎች በሙሉ እንኳን ከዘመነ ዮሐንስ ወደ ዘመነ ማቴዎስ በሠላምና በጤና አደረሳችሁ ። አዲሱ ዓመት የሠላም ፣ የፍቅርና የስኬት እንድሆንልን ልባዊ ምኞቴን እገልፃለሁ። በድጋሚ ለመላው አባላትና ደጋፊዎች በሙሉ መልካም አዲስ ዓመት እንዲሆንላችሁ እመኛለሁ ። የጎፋ ዕድገትና ልማት ማህበር ዋና ጽ/ቤት መስከረም 1/2017 ዓ.ም
ጎዕልማ ፎሪአፍርካ(ForAfrika) ከሚባል ግብረሰናይ ድርጅት ጋር አብሮ ለመሥራት የልማት ትብብር ውል ተፈራረመ። ይህ ግብረሰናይ ድርጅት በአካባቢ ጥበቃ፣ በውኃ፣ በምግብ ራስን መቻል፣ የአደጋ ስጋት ሥራዎች ላይ የምሠራ ሲሆን አሁን ከማህበራችን ጋር በአካባቢ ጥበቃ እና በምግብ ራስን መቻል ላይ ትኩረት አድርጎ ለመሥራት የውል ሰነድ ተፈራርሟል። ማህበራችን አቅም በፈቀደው በትምህርት ፣በጤና፣ በሰብዓዊ ፣ በባህል እና በማህበራዊ ዘርፎች በርካታ…
አቶ #አሸብር_ብሪሀኑ በ2016 ትምህርት ዘመን በወላጆች በዓል ላይ ተገኝተው ቃል የገቡትን ለሉጼ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የተለያዩ ማጣቀሻ መጽሐፍት ድጋፍ አድርገዋል። የሉጼ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የመማር ማስተማር ተግባር ውጤታማ እንዲሆን የዞኑ ተወላጆችና የጎፋ ዕድገትና ልማት ማህበር ደጋፊዎች የበኩላቸውን ድጋፍ እንዲያደርጉ ዋና ሥራአስኪያጁ ጥሪውን ያቀርባል።
ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ የጎፋ ዕድገትና ልማት ማህበር በአባቢው ላይ እያከናወነ ያለውን ልማታዊ ተግባራትን በዘላቂነት ለማገዝ ያስችል ዘንድ የልማት ማህበሩ #የቦርድ_አባላት (ሥራ አስፈፃሚ ዎች) ባቀረቡት ጥያቄ መሠረት የ15 ሚሊዮን ብር ድጋፍ ተደርጓል። የሚዲሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ተወካይ አቶ ያዕቆብ ፍቄ ተቋማቸው የጎፋ ዕድገትና ልማት ማህበር በዞኑ በመንግሥት የማይሸፈኑ የልማት ሥራዎችን እየሠራ ያለ ማህበር በመሆኑ ልማት ማህበሩን ለማጠናከር…
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጎፋ ዞን ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሻቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት አደጋ ጉዳት የደረሰባቸውን ወገኖች ለማቋቋም የድጋፍ ማሰባሰቢያ መድረክ በአዲስ አበባ ተካሄዷል፡፡ በአደጋው ሕይወታቸው ላጡ ዜጎች የ40 ቀን መታሰቢያና ከአደጋው የተረፉ ወገኖችን በዘላቂነት ለማቋቋም የሚያግዝ የገቢ ማሰባሰቢያ እንዲሁም አደጋውን ተከትሎ ኢትዮጵያውያን ላደረጉት ድጋፍ የምስጋና መድረክ ነው በመዲናዋ የተካሄደው፡፡ የድጋፍ ማሰባሰቢያና የምስጋና…
Don’t miss our future updates! Get Subscribed Today!